Sunday, 14 June 2015

ኢትዮ..…አማራ



ትዮ..…አማራ

ሰንደቃላማችን ከፍ ሲል ለዓለም
ሰማሁሽ ስትይ ኢትዮጲያዊ ቀለም
በራስሽ ፈጠራ ቀለሙን ቀማሚ
መሰረቱን ንደሽ ጣሪያዉን ልታቆሚ
………………እዉነትን ስታሚ
………………..ቅጥፈትን ስትሰሚ
ደምቆ እንዳይታይ ኢትዮጲያዊ ቀለም
ጦሰኛዋ  አንቺ ነሽ ሌላ ምክኒያት የለም
ትግሬ ነዉ ኦሮሞ?
ወላይታ ሲዳሞ?
አፋር ነዉ አደሬ?
በትምከት ፉካሬ
ማነዉ ያመሰዉ አገሬን?
እንዳንቺ አስተምህሮት
አንቺና ኢትዮጲያ ብቸኛ ወዳጂ
ሌላዉ ታዛቢ ነዉ ሊያዉም በግዳጅ
ዜግነት ለማግኘት ያንቺ መመዘኛ
ከቤሔር አማራ ከቋንቋ አማረኛ
ተፈጥሮ ብትከዳሽ ሆነሽ ነጭ ደሃ
ከእንስራሽ ብታጪ የምትጠጭዉ ዉሃ
የታሪክ አሻራ ድንጋዩን ክበሺ
ማንም ሳይደርስብሽ የምትናከሺ
በቅጥፈት ብዕርሽ ከትበሽ ከብራና
የእዉነት ጀንበር ወጥታ ሲገለጥ ገመና
ቀለሙም ተነነ…..……….ታሪኩም ተናደ
……………………………….ሳይቀር ለናሙና
የተካበ ድንጋይ ሲተረክ ለዓለም
ተንዶ አገኘሁት ኢትዮጵያዊ ቀለም
እንደሕዝባችን ፍቅር ጎልቶ እንዳልደመቀ
የትምክህት ምሶሶ በጉራ ወደቀ
አንድነት አይመጣም በከንቱ ፉከራ
ጥላቢስ እያለ ኢትዮ……..…… ተራራ
…………………….ኢትዮ…………... አማራ

ከዶኒ ዳን…የግጥም ማህደር…

No comments:

Post a Comment