Thursday, 12 May 2016

ተሹመዉ በጡንቻ አገርን ሲመሩ



አኪራ ታተመ

ተሹመዉ በጡንቻ አገርን ሲመሩ
ሲያነሱ ሲጥሉ ዝተዉ ሲፎኩሩ
ከአናታችን ነግሰዉ
ያለፊደል ደርሰዉ
ሳይጋግሩ ጎርሰዉ
በጠባቂ ታጥረዉ
ተጠርጣሪን አስረዉ
ከሞት ሲሸሸጉ
ምነዉ ተገደዱ
ጊዜ የማይመርጠዉ ቀን ይሁን ጨለማ
ቅርፁ የማይታየዉ ድምጡ የማይሰማዉ
ዘልቆ ገባ አሉኝ ከቤተ መንግስቱ
እኔንስ ገረመኝ አለማንኳኳቱ
በሞት ተሸንፈዉ በፍተሐዊ ምርጫ
ሊቀርቡ ነዉ አሉኝ ሰማይ ቤት ፍጥጫ
ተቃዋሚ ሳይኖር ምነዉ አጡ ማምለጫ
ተብትበዉ ጠምጥመዉ አገሬን ሲገዙ
ከተግባርም ርቀዉ በህልሞትም ሲያዙ
ምን አሉ በሞቴ ተገደዉ ሲጓዋዙ
አልተከራከሩም
ጋርዶች አልነበሩም
ቆይ ምንድነዉ ጉዱ
እንዲሁ ሲገደዱ
ነብሶ ስትነጠቅ ስዉር ሲዳበሱ
በሽጉጥ አናቱን ምነዉ ሳያፈርሱ
በፀረ-ሽብሩ ህግ ለምንስ ሳይከሱት
አኛን ተሳናብተዉ መቃብር ሲወርዱ
በሰላም ደርሰዋል እንዴት ነዉ መንገዱ
ማነዉ የተቀበሎት አበባ ታቅፎ
በሱፍ  ሽክ ብሎ በወግ ተሰልፎ
ምን አዩ በሞቴ በድቅድቅ ጭለማ
ምሽት እንዴት ነበር የቀብር ዋዜማ
ከማያዉቁት አገር ከሄዱበት መንደር
ሲገለጥ መፀሀፉ የእዉነት ማህደር
ምላስም ታሰረ
ጉልበት ተሰበረ
ብልጠትም ከሰረ
ክብሮትም ወደቀ
ማንነት ደቀቀ
ሁሉም አከተመ…
የደረሱት መፀሀፍ
… አኪራ ታተመ

No comments:

Post a Comment